ማክሰኞ 2 ሴፕቴምበር 2025

ስብከከት

 ጴጥሮስንና ከእርሱ ጋር የነበሩት እንቅልፍ ከበደባቸው፤ 


የሉቃስ ወንጌል 9፥32 


ከዚህም ቃል በኋላ ስምንት ቀን ያህል ቈይቶ ጴጥሮስንና ዮሐንስን ያዕቆብንም ይዞ ሊጸልይ ወደ ተራራ ወጣ። ሲጸልይም የፊቱ መልክ ተለወጠ፤ ልብሱም ተብለጭልጮ ነጭ ሆነ።  እነሆም፥ ሁለት ሰዎች እነርሱም ሙሴና ኤልያስ ከእርሱ ጋር ይነጋገሩ ነበር፤ በክብርም ታይተው በኢየሩሳሌም ሊፈጽም ስላለው ስለ መውጣቱ ይናገሩ ነበር።  ነገር ግን ጴጥሮስንና ከእርሱ ጋር የነበሩት እንቅልፍ ከበደባቸው፤ ነቅተው ግን ክብሩንና ከእርሱ ጋር ቆመው የነበሩትን ሁለት ሰዎች አዩ። ከእርሱም ሲለዩ ጴጥሮስ ኢየሱስን፦ አቤቱ፥ በዚህ መሆን ለእኛ መልካም ነውና አንድ ለአንተ አንድም ለሙሴ አንድም ለኤልያስ ሦስት ዳሶች እንሥራ አለው፤ የሚለውንም አያውቅም ነበር።  ይህንም ሲናገር ደመና መጣና ጋረዳቸው፤ ወደ ደመናውም ሲገቡ ሳሉ ፈሩ። ከደመናውም፦ የመረጥሁት ልጄ ይህ ነው፥ እርሱን ስሙት የሚል ድምፅ መጣ። ድምፁም ከመጣ በኋላ ኢየሱስ ብቻውን ሆኖ ተገኘ። እነርሱም ዝም አሉ ካዩትም ነገር በዚያ ወራት ምንም ለማንም አላወሩም። ሉቃ 9÷28-37 


የደብረ ታቦር በዓል ጌታችን ምሥጢረ መለኮቱን የገለጠበት፤ ብርሃን የታየበትና ድምፀ መለኮቱ የተሰማበ ዕለት ነው፡፡ 


ለደብረ ታቦር ኩነት እንደ ዐበይት ምክንያት አድርገን የምንወስደው ጌታችን እና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የሚከተሉትን ደቀመዛሙርቱን በቄሳርያ አካባቢ ሲደርሱ የጠየቃቸው ጥያቄ ነው ቅዱስ ማቴዎስ በወንጌሉ እንዲህ ጽፎታል፡፡  


ኢየሱስም ወደ ፊልጶስ ቂሣርያ አገር በደረሰ ጊዜ ደቀ መዛሙርቱን፦ ሰዎች የሰውን ልጅ ማን እንደ ሆነ ይሉታል? ብሎ ጠየቀ።  እነርሱም፦ አንዳንዱ መጥምቁ ዮሐንስ፥ ሌሎችም ኤልያስ፥ ሌሎችም ኤርምያስ ወይም ከነቢያት አንዱ ነው ይላሉ አሉት። እርሱም፦ እናንተስ እኔን ማን እንደ ሆንሁ ትላላችሁ? አላቸው። ስምዖን ጴጥሮስም መልሶ፦ አንተ ክርስቶስ የሕያው እግዚአብሔር ልጅ ነህ አለ። 

ኢየሱስም መልሶ እንዲህ አለው፦ የዮና ልጅ ስምዖን ሆይ፥ በሰማያት ያለው አባቴ እንጂ ሥጋና ደም ይህን አልገለጠልህምና ብፁዕ ነህ። ብሎታል፡፡ (ማቴ 16፡13-20) 


ቅዱስ ጴጥሮስ በመንፈስ ቅዱስ ገላጭነት የመሰከረውን ምስክርነት ከአብ ከመንፈስ ቅዱስ ይሰሙ ዘንድ፣ ከነቢያት (ሙሴና ኤልያስ) አንደበት ይረዱ ዘንድ፣ጴጥሮስ፣ ያዕቆብና ዮሐንስን  ወደ ደብረ ታቦር ተራራ ይዞቸው ወጣ፡፡ (ማቴ 17፡1-10) 


ቅዱስ ማቴዎስ እና ቅዱስ ማርቆስ ፊልጶስ ቂሣርያ አገር ቅዱስ ጰጥሮስ የተናገረበትን ቀን እና  የደብረ ታቦር ተራራ ድርጊት የተፈጸመበትን ቀን ቆጥረው ስድስት ቀን በኃላ ብለው ሲጽፉ ቅዱስ ሉቃስ ደግሞ በፊልጶስ ቂሣርያ ድርጊቱ ከተጀመረበት አንስቶ እስከ ደብረ ታቦር መገለጥ ያሉትን ቀኖች በሙሉ በመቁጠር ስምንት እንዳደረሰው ሊቃውንተ ቤተክርስቲያን ያስረዳሉ፡፡ 


መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ዘጠኙን ሐዋርያት በተራራው ሥር ትቶ ለምን ቅዱስ ጴጥሮስን ቅዱስ ያዕቆብን እና ቅዱስ ዮሐንስን ለምን መርጦ ወደ ደብረ ታቦር ተራራ ላይ አውጥቶ ብርሃነ መለኮቱን ገለጠላቸው ለሚለው ጥያቄ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ እንዲህ ይመልስልናል፡፡ 


  ‹‹ቅዱስ ጴጥሮስ ፍቅሩን በተደጋጋሚ በመናገር ገልጿል ፡፡ ቅዱስ ዮሐንስም  ለመድኃኒታችን የተለየ ፍቅር  እንዳለው በወንጌል ሳይቀር ‹ጌታን የሚወደው› ተብሎ ተነግሮለታል ፡፡ቅዱስ ያዕቆብ ከወንድሙ ጋር በመሆን በለመነው ልመና አንተ የምትጠጣውን ጽዋ እንጠጣለን እስከማለት የጠየቀ በመሆኑ  በማቴ 20፡22  በዚህ ምክንያት መርጦቸዋል ›› በሏል፡፡ 


በሐዲስ ኪዳን መጽሐፍ ቅዱስ ክፍል ውስጥ እግዚአብሔር አብ ለመጀመሪያ ጊዜ መድኃኒታችን በዮርዳኖስ ሲጠመቅ "እነሆም፥ ድምፅ ከሰማያት መጥቶ፦ በእርሱ ደስ የሚለኝ የምወደው ልጄ ይህ ነው አለ። " ማቴ 3፥17  በደብረታቦር ደግሞ ለሁለተኛ ጊዜ "ከደመናውም፦ የመረጥሁት ልጄ ይህ ነው፥ እርሱን ስሙት የሚል ድምፅ መጣ።"ሉቃ 9፥35  


የደብረ ታቦር ተራራን ወጥተው የተገኙት ሦስቱ ደቀመዛሙርት ምስጢረ መለኮት ተካፋይ ሲሆኑ ሲጸልይም የፊቱ መልክ ተለወጠ፤ ልብሱም ተብለጭልጮ ነጭ ሆነ።  


ታላቁን ምሥጢረ ሥጋዌ እግዚአብሔር ዓለምን የሚያድንበትን ጥበብ በሚነገርበት በብርሃን በተከበበ ተራራ ላይ ቅዱስ ጴጥሮስንና ከእርሱ ጋር የነበሩት እንቅልፍ ከበደባቸው በተለይም ቅዱስ ጴጥሮስ ሌሎቹን ሐዋርያት ዘንግቶ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስን በደብረታቦር ተራራ ላይ ዳስ ሠርቶ /ድንኳን ጥሎ / መኖር ይሻለናል ብሎ ጠየቀው ፡፡ 


ወንጌላዊያኑ ይህን የቅዱስ ጴጥሮስን ደካማ ጎን ገልጸውታል ቅዱስ ማርቆስ "እጅግ ስለ ፈሩ የሚለውን አያውቅም ነበር።" ሲል  (ማርቆስ 9፥6 )  ቅዱስ ሉቃሰ  ደግሞ  "የሚለውንም አያውቅም ነበር።"   ሉቃ 9፥33 በማለት ነቅፈውታል፡፡  ቅዱስ ጴጥሮስንና ከእርሱ ጋር የነበሩት እንቅልፍ ስለ ከበደባቸው ድምጹን መስማት አልቻሉም። ጌታችን የከበደባቸውን እንቅልፍ በችርነቱ አርቆላቸው ሙሴን እና ኤልያስን እንዲሁ መለኮታዊ ክብሩን ተመለከቱ።  


ከከበደበት እንቅልፍ በደንብ ያልነቃው ቅዱስ ጴጥሮስ ግን ከእርሱ ጋር ቆመው የነበሩትን ሁለት ሰዎች ከእርሱም ሲለዩ  ምድራዊ ጥያቄ አቀረበ። ይህንም ሲናገር ደመና መጣና ጋረዳቸው፤ ወደ ደመናውም ሲገቡ ሳሉ ፈሩ። ከደመናውም፦ የመረጥሁት ልጄ ይህ ነው፥ እርሱን ስሙት የሚል ድምፅ መጣ። ድምፁም ከመጣ በኋላ ኢየሱስ ብቻውን ሆኖ ተገኘ።        


ቅዱስ ጴጥሮስንና ከእርሱ ጋር የነበሩት እንቅልፍ የከበደባቸው በደብረ ታቦር ተራራ ላይ ብቻ አልነበር። ቅዱስ ማቴዎስ በ ወንጌሉ ፤ በጌቴ ሴኒ የሆነውን እንዲህ ጽፎታል በዚያን ጊዜ ኢየሱስ ከእነርሱ ጋር ጌቴሴማኒ ወደምትባል ስፍራ መጣ ደቀ መዛሙርቱንም፦ ወዲያ ሄጄ ስጸልይ ሳለ በዚህ ተቀመጡ አላቸው። ጴጥሮስንም ሁለቱንም የዘብዴዎስን ልጆች ወስዶ ሊያዝን ሊተክዝም ጀመር። ነፍሴ እስከ ሞት ድረስ እጅግ አዘነች፤ በዚህ ቆዩ ከእኔም ጋር ትጉ አላቸው። ጥቂትም ወደ ፊት እልፍ ብሎ በፊቱ ወደቀና ሲጸልይ፦ አባቴ፥ ቢቻልስ፥ ይህች ጽዋ ከእኔ ትለፍ፤ ነገር ግን አንተ እንደምትወድ ይሁን እንጂ እኔ እንደምወድ አይሁን አለ። ወደ ደቀ መዛሙርቱም መጣ፤ ተኝተውም አገኛቸውና ጴጥሮስን፦ እንዲሁም ከእኔ ጋር አንዲት ሰዓት እንኳ ልትተጉ አልቻላችሁምን? ወደ ፈተና እንዳትገቡ ትጉና ጸልዩ፤ መንፈስስ ተዘጋጅታለች ሥጋ ግን ደካማ ነው አለው። ደግሞ ሁለተኛ ሄዶ ጸለየና፦ አባቴ፥ ይህች ጽዋ ሳልጠጣት ታልፍ ዘንድ የማይቻል እንደ ሆነ፥ ፈቃድህ ትሁን አለ።  ደግሞም መጥቶ ዓይኖቻቸው በእንቅልፍ ከብደው ነበርና ተኝተው አገኛቸው። ቅዱስ  ማርቆስም  ደግሞም "መጥቶ ዓይኖቻቸው በእንቅልፍ ከብደው ነበርና ተኝተው አገኛቸው፥ የሚመልሱለትንም አላወቁም።" በማለት ይህንኑ ታሪክ ነግሮናል ። ማር 14፥40    


በጌቴ ሴማኒም ሆነ ደብረ ታቦር ምስጢረ መለኮት የተገለጠባቸው የብርሃን ድንኳን የሚተከልበት ሙሽራው ኢየሱስ ክርስቶስ የሚገኝባቸው ድምፁን የምንሰማበት የክብር ቦታ የቤተ ክርስቲያን  ምሳሌዎች ናቸው። 


በዚህ ስፍራ ተገኝተው ከመንፈሳዊ ይልቅ ሥጋዊ ከሰማያዊ ይልቅ ምድራዊ ሀሳብ የሚቀባጥሩ ሰዎች እንቅልፍ የከበደባቸው ሰነፎች ናቸው።በሠርግ ቤት ተገኝተው ሙሽራው አይመጣም ብለው እንደተኙት ሰነፍችን ይመስላል  "ሙሽራውም በዘገየ ጊዜ ሁሉ እንቅልፍ እንቅልፍ አላቸውና ተኙ። " የማቴዎስ ወንጌል 25፥5  እንቅልፍ የከብድባቸው ሰዎች ሰነፎች ናቸው ጠቢብ ሰሎሞንም  "አንተ ታካች፥ እስከ መቼ ትተኛለህ? ከእንቅልፍህስ መቼ ትነሣለህ?  ይላል ። ምሳ 6፥9  ቅዱስ ጳውሎስም "ከእንቅልፍ የምትነሡበት ሰዓት አሁን እንደ ደረሰ ዘመኑን እወቁ፤ ካመንንበት ጊዜ ይልቅ መዳናችን ዛሬ ወደ እኛ ቀርቦአልና።"ወደ ሮሜ ሰዎች 13፥11  ይለናል። 


በቅዱሱ ተራራ ከፍ ብለን ከተገኘን ከእንቅልፍ ነቅተን ለጽድቅ ለመንግስተ ሰማያት ለሚያበቃ ሥራ እንትጋ።      


            ይቆየን 


            ያዕቆብ ሰንደቁ 

     ነሐሴ 13 ቀን 2017 ዓ/ም

              አዲስ አበባ።

ረቡዕ 28 ፌብሩዋሪ 2024

ስበከት

 

ባለ ዕዳ ልጆቼን ባሪያዎች አድርጎ ሊወስዳቸው መጥቶአልመጽሐፈ ነገሥት ካልዕ 4 1

በዲ/ን ብርሃኑ አድማስ ከዓመታት በፊት በሚሊንየም አዳራሽ ያስተማረው ትምህርት ነው፡፡ ትምህርቱን ስትሰሙት ለዛሬ ጊዜ የቤተክርስቲያን ፈተና ሁሉ ምላሽ የሚሰጥ ፤የሐዲስ ኪዳን ጥላ በሆነው በቡሉይ ኪዳን ዘመን በተፈጸመ ታሪክ ውስጥ፤ የአሁን ዘመን የቤተክርስቲያ ፈተና የሚያሳይ፤  ዲያቢሎስ ልጆቿን ባለዕዳ አድርጎ ሊወስድ ቢሞክርም እንደማይችል፤ ጊዜው ሲያልፍ ፈተናውም እንደሚያልፍ፤ ቤተክርስቲያን የመንፈስ ቅዱስ የጸጋው ግምጃቤት ሆና እንደምትኖር የሚያስረዳ የሚያጽናና ትምህርት ነው፡፡

ከታች ያለውን ማስፈንጠሪያ ተጭነው ይህን ስብከት ያዳምጡ

https://youtu.be/ahg57DS5UP4

3፡28᎓-  መጥታም ለእግዚአብሔር ሰው ነገረችው እርሱም ሄደሽ ዘይትሽን ሽጪ ለባለዕዳውም ክፈይ አንቺና ልጆችሽም ከተረፈው ተገመገቡ አለ

5፡56᎓-  መጽሐፍ ቅዱስ ስናነብ የእሥራኤል መንግስት የሚለው የአሥሩን ነገድ መንግስት ነው፡፡

6፡45᎓- በብሉይ ኪዳን ጊዜ መቅደሱ አንድ ብቻ ነው እርሱም ኢየሩሳሌም ነው በየአውራጃው በየወረዳው የነበረው ሙክራብ ይባላል::

8፡36᎓- አክአብ በጣም ጨካኝ ሚስቱ ኤልዛቤል በትውልዷ ሶርያዊት  ስለነበረች  እግዚአብሔርን ስለማምለክ ከፍተኛ ጥላቻ ነበራት::

10፡02᎓- በዚያን ዘመን ነቢዩ ኤልያስ ነበረ የእግዚአብሔር አምላክነት እንዲታወቅ ሰማይን እና ምድርን ገዘተ::

10፡42᎓- አቡዲዩ የአክአብ ባለሥልጣን ሆኖ በአክአብ ቤተመንግስት እየኖረ መቶ ነቢይነት ትምህርት የሚማሩ ደቀመዛሙርትን ሃምሳውን በአንድ ዋሻ  ሃምሳውን በአንድ ዋሻ  ብቻውን ደብቆ  ማስተማር መመገብ ጀመረ::

17፡36᎓- ባሌ ባርያህ ሞቷል እግዚአብሔርን ይፈራ እንደነበረ አንተ ታውቃለህ::

26፡26᎓- ወደ ኤልሳ የሄደቸው ሴት የቅድስት ቤተ ክርስቲያን ምሳሌ ናት ኤልሳ ደግሞ የጌታችን የአምላካችን የኢየሱስ ክርስቶስ ምሳሌ ነው ልጆቿ ደግሞ የምእመናን ምሳሌዎች ናቸው ባለ ዕዳ የተባለው ደግሞ ዲያብሎስ ነው

28፡23᎓- ቤተክርስቲያን ልጆቿን ለመሥጠት ፈቃደኛ አይደለችም ምንም ያህል ባለእዳዎች ብንሆንም ምንም ያህል ኃጢአተኞች ብንሆን::

ሰኞ 8 ጃንዋሪ 2024

ካነበቡኩት

 


 ልጃቸውን በስለት ለቤተ ክርስቲያን የሰጡት ፊሊፒንሳዊው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ካህን

   የፎቶው ባለመብት, Dante Alonzo/ Alemayhu Zenebe

የምስሉ መግለጫ,  ቀሲስ ዳንቴና ዲያቆን ዮሐንስ 6 ጥር 2024

ዳንቴ አሎንዞ ካህን ናቸው።  አገልግሎታቸው በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ነው።  በቤተ ክርስቲያኒቱ ለጥቂቶች ብቻ የተፈቀደውንም ምስጢር ያውቃሉ። ሁለተኛ ቄስ ሆነው ቅዳሴ ይመራሉ። ከቅዳሴ በኋላ ምዕመናንን ያቆርባሉ። ታቦት ይይዛሉ። ሌላም ሌላም አገልግሎት ይሰጣሉ። ተወልደው ያደጉት በሩቅ ምሥራቋ አገር ፊሊፒንስ ነው።

ፓኒኪ ታርላ በተሰኘችው ከተማ ልጅነታቸውን አሳልፈዋል። በዚያች ከተማ ጎዳናዎች ላይ ከጥቂት አስርት ዓመታት በፊት ዳቦ ይሸጡ ነበር። የዳቦ ንግዳቸውን ጠዋት ጨርሰው ከሰዓት ማርሻል አርት ይማራሉ። አብዛኛው የልጅነት ጊዜያቸው እንዲህ ነበር ያለፈው።

ያኔ ኢትዮጵያ የምትባል አገር፣ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ የሚባል ሃይማኖት ስለመኖሩ አያውቁም።  ለነገሩ በፊሊፒንስ የኦርቶዶክስ ክርስትና ብዙም አይታወቅም። በአገራቸው ከፍተኛ ቁጥር ያለው ሕዝብ የሮማ ካቶሊክ እምነት ተከታይ ሲሆን፣ እስልምና ሁለተኛውን ደረጃ ይይዛል።

ፊሊፒንስ እያለሁ ስለ ኦርቶዶክስ ክርስትና ፍጹም ሰምቼ አላውቅምይላሉ። ታዲያ ዳንቴ የኢትዮጵያ ኦርቶክስ ተዋህዶን ከማወቅ አልፈው አገልጋይ ለመሆን እንዴት በቁ? እሳቸው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ተከታይ የሆንኩበት አጋጣሚእጅግ የሚገርመኝ እና ተዓምር ነውሲሉ ይገልጹታል።

አንድ ቀን፣የእግዚአብሔርን መንግሥት ለማወቅመጽሐፍ ቅዱስ ገልጠው ማንበብ ጀመሩ።  መጽሐፍ ቅዱስ ሲያነቡ የመጀመሪያቸው ነበር። በመጀመሪያዎቹ ገጾች ልባቸውን የያዘ ቃል አገኙ።  ኦሪት ዘፍጥረት ምዕራፍ 2 ቁጥር 13 ላይ ያለው ጥቅስቀልቤን ገዛውይላሉ። ያ የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍልምየሁለተኛውም ወንዝ ስም ግዮን ነው፤ እርሱም የኢትዮጵያን ምድር ሁሉ ይከብባልይላል። ይህ አጋጣሚ ስለኢትዮጵያ ለማወቅ ጉጉትን ፈጠረባቸው። ይህ ሲሆን ወደ ካናዳ ተሰደዋል።

በምኖርበት ቶርንቶ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያንን ማፈላለግ ጀመርኩሲሉ ይገልጻሉ። ከብዙ ፍለጋ በኋላ፣ በካናዳ ጃማይካውያን በአውሮፓውያኑ 1977 ያቋቋሙት መድኃኒዓለም የተሰኘ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክስርስቲያንን አገኙ። ከቤተ ክርስቲያኑ ደጃፍ ቆመው አንኳኩ።  ምላሽ ግን አልነበረም። ስልክ ደወሉ። በቀጣዩ ሳምንት እንዲመጡ ተነገራቸው። ጥሩ አጋጣሚሆኖ ቀን በኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን የክርስቶስ ትንሳኤ የሚከበርበት ምሽት ነበር።  በዚያን ጊዜ ካቶሊክ ነበርኩ። አንድ ሳምንት ቀደም ብዬ በካቶሊካውያን የሚከበረውን ትንሳኤ አክብሪያለሁሲሉ ያስታውሳሉ።

የሆነው ሆኖ በዚያች የፋሲካ ምሸት በካናዳ የሚገኘው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ደረሱ።  ልክ ስደርስ ሥርዓተ አምልኮቱ ተጀምሮ ነበር። በሕይወቴ በጣም ስሜቴ የተነካው ያኔ ነው። ምንም የማውቀው ነገር ባይኖርም፣ ይህ ትክክለኛ ቦታ ነው አልኩ። በመጀመሪያ ቅጽበት የነበረኝ ስሜት በጣም ጠንካራ ነበርይላሉ።

ያዩት ሥርዓተ አምልኮ ለእሳቸው ፍጹም አዲስ ቢሆንም፣ ቋንቋው ባይገባቸውም ነገሩ በሕይወታቸው ትልቅ ለውጥ ይዞ እንደሚመጣ ግን ተገንዘበውታል። ይህ የእኔ ቤተክርስቲያን ነው አልኩ። ሥርዓተ አምልኮቱ ሲጀምሩ፣ ማልቀስ ጀመርኩ። ልክ ሕጻናት እንደሚያለቅሱት ነው ያለቀስኩት። በጣም ስሜታዊ ሆኜ ነበር። እግዚአብሔርን አላውቅም ነበር አልኩኝ።

በዚያው ቀን አንድ ምዕመን ስለኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ታሪክ የሚያትት መጽሐፍ እንደሰጣቸው ያስታውሳሉ።   መጽሐፍ ብዙ ረድቷቸዋል። ከጊዜ በኋላም የኢትዮጵያ ኦርቶክስ ተዋህዶ እምነትን ተቀብለው ተጠመቁ። ገብረ መድኅን የሚል የክርስትና ስምም ተሰጣቸው።

 

የቤተክርስቲያን አገልግሎትን የጀመርኩት ከጽዳት ነው

ዳንቴ የኦርቶዶክስ ክርስትናን ተቀብለው ብቻ አላቆሙም። የቤተክርስቲያኒቱን የአምልኮ ሥርዓት መማር ጀመሩ።   በእንግሊዝኛ የተዘጋጁ መጻህፍትን ያነባሉ።   አባ ደስታ ከተባሉ አባት የኦርቶዶክስ አስተምህሮቶችን፣ ሥርዓተ አምልኮን፣ ታሪክን እና ሌሎች መጽሐፍትን ለሁለት ዓመታት ተማሩ።  አባ ደስታ ለእሳቸው ብቻ ሳይሆን በካናዳ ለሚገኙ የኦርቶዶክስ ተዋህዶ ተከታይ ጃማይካውያን ትህምርትን ይሰጡ ነበር።

እሳቸው 1993 .. ከካናዳ ሲወጡ፣ ቀሲስ ዳንቴ እስካሁን ድረስ እያገለገሉ ወደሚገኙበት በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን የቶሮንቶ ቅድስት ማርያም ካቴድራል አመሩ።  ወደዚህ ቤተክርስቲያንየማይመጣ የውጪ ዜጋ የለም።ስለኢትዮጵያ የሰሙ ወይም ያነበቡ የውጭ አገራት ዜጎች ይመጣሉ፤ ይጠይቃሉ። ማገልገል እንፈልጋለን ይላሉ። ይህ የተለመደ ነው።  ችግሩ የሚዘልቁትእጅግ በጣምጥቂቶቹ ናቸው።  ብዙዎች ይመጣሉ። ቋንቋው እና ባህሉ አዲስ ሲሆንባቸው ተመልሰው ይሄዳሉይላሉ አቶ ዓለማየሁ።

አቶ ዓለማየሁ ዘነበ በቤተክርስትያኑ 32 ዓመታት አገልግለዋል።  በቶሮንቶ ዩኒቨርሲቲ በሥነ መለኮት የተመረቁ ሲሆን፣ አሁን ላይ የመንበረ ብርሃን ቅድስት ማርያም ካቴድራል ጽህፈት ቤት ኃላፊ ናቸው። ዳንቴ አሎንዞንም በደንብ ያውቋቸዋል።  ከጥቂት ጊዜያት በኋላ ዳንቴ መጥተው እንደሚመለሱት ሌሎች የውጭ አገራት ዜጎች እንዳልሆኑ ተረዱ። የሚመላለሱበት ድግግሞሽ፣ ትህትናቸው እና ትጋታቸው የተለየ ሆኖ አገኙት።  እኛ ይህን ሁሉ ስናይይሄ ሰውዬ ለካ የምሩን ነውአልን. . . ለቤተክርስቲያን ልዩ ፍቅር እና ታማኝነት አለው። ከሰው ጋር ተግባቢ ነው። ቤተሰቡንም ይዞ ይመጣ ነበር። ልጆቹም እዚህ ካሉት ልጆች ጋር ወዲያው ነበር የተግባቡት። እኛም በትልቅ ደስታ ነበር የተቀበልነውሲሉ ይናገራሉ።

የፎቶው ባለመብት, Alemayhu Zenebe

የምስሉ መግለጫ, ቀሲስ ዳንቴ በዲቁና በሚያገለግሉበት ወቅት

የቤተክርስቲያኒቱ አግልግሎት በግዕዝ እና በአማርኛ መሆኑ የቀሲሱ ዳንቴን የአገልግሎት ጉዞ ፈታኝ አድርጎታል።

ቢሆንም አገልግሎታቸው ቀጥሏል።  እውነትን እንዳገኘሁ ሲገባኝ በቤተ ክርስቲያን ውስጥ የምችለውን አገልግሎት ለመስጠት ወሰንኩኝ። በእኔ አቅም ሊሠራ የሚችል ሥራን መሥራት ጀመርኩ። ጽዳት እና ምግብ የሚያበስሉትን ማገዝ ጀመርኩ። ስፈልገው የነበረውን እውነት ስላገኘሁ ቤተ ክርስቲያንን የሕይወቴ አንድ አካል አደረኳትሲሉ ይገልጻሉ።

ከዓመታት የትምህርት እና የቤተክርስቲያን አገልግሎት በኋላ ድቁናን እንዲቀበሉ መወሰኑ ተነገራቸው። አላመኑም።በወቅቱ የተፈጠረብኝን ስሜት ቃላት አይገልጸውምይላሉ። በዚህ መካከል የተወለዱት ሁለት ልጆቻቸውን ወደ ቤተክርስቲያን ሁልጊዜ ይዘዋቸው ይመጡ ነበር።  ልጆቹ መዘምራን ክፍል ውስጥም ገብተዋል። ዮሐንስ [ወንዱ ልጃቸው] የሦስት ዓመት ልጅ እያለ [አባቱ] ትንሽ ከበሮ ሰርቶለት ሁልጊዜ ከፊት ቆሞ ይዘምር ነበርሲሉ አቶ ዓለማየሁ ይናገራሉ።

የዳንቴ ክህነት እና አገልግሎት

ዳንቴ ግንቦት 3/ 2008 .. ድቁናን ከአቡነ መቃሪዮስ ተቀበሉ።

ይኼኔ ዕድሜያቸው 39 ዓመት ነበር።

ድቁናን ሲቀበሉ እጅግ ደስ ብሏቸዋል። ደስ ቢላቸውምይህ ለእኔ አይገባም፣ ብቁ አይደለሁምብለውም ነበር።

እዚህ ደረጃ ለመድረስ ከሊቀ ካህናት ምሳሌ እንግዳ እና ከሌሎች መምህራን ለዓመታት ለድቁና የሚያበቃቸውን ትምህርት በእንግሊዝኛ ተምረዋል።  ለአገልግሎት ብቁ እንደሆኑ ሊቀ ካህናት እንግዳ ምስሌ ትልቅ አስተዋጽኦ እንደላቸው ይናገራሉ።

ለዚህ ሥርዓት አዲስ ስለሆንኩ ብዙ ነገር አላወቅም ነበር የሚሉት ዳንቴበእያንዳንዱ ነገርቀጥሎ ምን ላድርግ?’ እያልኩ እጠይቅ ነበርሲሉ ይገልጻሉ።   አቶ ዓለማየሁ ደግሞበጣም ትሁት ሰው ስለሆነ የሚያወቀውን ለመናገር አይደፍርም። ለዚያ ብቁ መሆኑ ከታመነ በኋላ ነው ወደ ድቁና እንዲሄድ የተደረገው. . . ለቤተክርስቲያን ትጉህ እና ታማኝ ነውሲሉ ይመሰክሩላቸዋል።

በግዕዝ እና በአማርኛ የተጻፉ ግን በላቲን ፊደል የተቀረጹ መጻህፍትን አጥንተዋል።  ቋንቋውን ለመናገር ይቸገሩ እንጂ አንዳንድ መጽሐፍትን በቃላቸው ይዘዋል።  በዚህ ሁኔታ፣ በተለይ በእንግሊዝኛ የቤተ ክርስቲያንን አግልግሎት መስጠት ጀመሩ።  በዚህ ጊዜ የዳንቴ አራተኛ ልጅ በዚያው ቤተክርስቲያን የድቁና ትምህርትን ከሌሎች ሕጻናት ጋር እየተከታተለ ነበር።  ይህ ከሆነ ልክ 10 ዓመታት በኋላ የዳንቴ የዲያቆንነት አገልግሎት አበቃ።  ቅስናን ለመቀበል እና ቀሲስ ለመባል ተመረጡ።  የጠበቁት ግን አልነበረም።

የቤተክርስቲያኑ አስተዳዳሪ መጥተው ቄስ ልትሆን ነው ሲሉኝ። ደነገጥኩዝግጁ አይደለሁም እኮስላቸውልጅህ ዲያቆን ሊሆን ነው። አንተም እሱም ዲያቆን መሆን አትችሉም፣ ይህ የቤተክርስቲያንን ሕግ ይጻረራል አሉኝእንኳን ለቅስና ለድቁናው እኮ በደንብ አልበቃሁም አልኳቸው’ ” ይላሉ።  የሆነው ሆኖ፣ ሚያዚያ 28/ 2010 .. ቅስናን ተቀበሉ። ቀሲስ ዳንቴ (ቀሲስ ገብረ መድኅን) ተባሉ።  

እውነት ለመናገር ይህ ለእኔ ትልቅ ነገር ነው።በዚህ ባህል ውስጥ አላደግኩም። ዕድገቴ በምዕራባውያኑ ባህል ውስጥ ነውየሚሉት ቀሲሱለዚህ አልገባምቢሉም የተሰጣቸውን ኃላፊነት ተቀበሉ።  ቀሲስ ዳንቴ በቅዳሴ ወቅት ረዳት ወይም ሁለተኛ ቄስ በመሆን ሥርዓቱን ይመራሉ። ከቅዳሴ በኋላ ምዕመናንን ያቆርባሉ።

በክብረ በዓላት ወቅት ደግሞ ታቦት ይይዛሉ።  ለመጀመሪያ ጊዜ ታቦት እንዲይዙ ሲነገራቸውይህንን ለማድረግ ብቁ አይደለሁምብለው ተከራክረዋል።  ግድ መሆኑን ስረዳ፣ ፈጣሪ ይቅር በለኝ። እኔ ይህንን ለማድረግ አልበቃሁም አልኩኝይላሉ።  በተጨማሪም በቅዳሴ ወቅት የወንጌል ንባቦችን በእንግሊዝኛ ያነባሉ። በግዕዝ እና በአማርኛ ቋንቋ ክርስትና ለማንሳት እና ለማጥመቅ እየተማሩም ነው።  ለአንዳንድ የእንግሊዝኛ ተናጋሪ ምዕመናን መንፈሳዊ አባታቸውእንደሆኑ አቶ ዓለማየሁ ጠቅሰዋል። ከዚህም ውጪ በእጅ ሙያቸው ቤተ ክርስቲያንን ያግዛሉ።  ካህናት፣ ዲያቆናት እና ምዕመናን በፍቅር ነው የሚያዩዋቸው እንጂ መጠራጠር እና አይችሉም ብሎ ማሰብ የለምበማለትም አቶ ዓለማየሁ ይናገራሉ።

ዲያቆን ዮሐንስ አሎንዞ፡ በስለት የተሰጠው ልጅ

የፎቶው ባለመብት, Alemayhu Zenebe

የምስሉ መግለጫ, ዲያቆን ዮሐንስ አሎንዞ (ከመሐል)

ዳንቴ 1971 .. ልክ 16 ዓመት ሲሞላቸው የተወለዱበትን፣ ያደጉበትን ዳቦ የሸጡበትን የፊሊፒንስ መንደሮች ጥለው ወደ ካናዳ ተሰደዱ።  ከዚያ ጊዜ ጀምሮ ኑሯቸው ካናዳ ሆነ።  ቤተሰባቸው ትልቅ ነው - 13 ወንድም እና እህት አላቸው።  ወደ ካናዳ የተሰደዱት ግን እሳቸውን ጨምሮ ሰባት የቤተሰቦቻቸው አባላት ናቸው። ከ28 ዓመታት በፊት 1988 .. ትዳር መሠረቱ።  ጋብቻቸው በካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን ሥርዓት ካናዳ ውስጥ ነበር የተፈጸመው።

ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ጋር ከመተዋወቃቸው በፊት የተወለዱት ሦስት ልጆቻቸውም በካቶሊክ ቤተክርስቲያን ውስጥ ተጠምቀዋል።  ከዚያ በኋላ የተወለዱት 2 ልጆች ግን በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ሥርዓት የክርስትና ጥምቀት ተደርጎላቸዋል። ዮሐንስ እና ማክዳ የሚል ስምም ተሰጥቷቸዋል። ቀሲስ ዳንቴ ወደዚህ ሕይወት ከመጡ በኋላ ወንድ ልጃቸው ዮሐንስ ከቤተክርስቲያን ጋር የተለየ ቁርኝት እንዲኖረው ወሰኑ።

20 ዓመታት በፊት የሆነውን ልክ ዛሬ እንደሆነ ያስታውሱታል። ኦርቶዶክስን በተቀልኩበት የመጀመሪያዎቹ ጊዜያት ዮሐንስ የጸሎቴ ሁሉ አካል ነበር።ፈጣሪ ወንድ ልጅ ስጠኝ። ስሙን ዮሐንስ ብዬ አንተን እንዲያገለግል እሰጠዋለሁስል ለመንኩ። ይህ ከሆነልኝ ወደ ኢትዮጵያ እሄዳለሁ [ብዬ ተሳልኩ] አልኩ። ይገርማል፣ ፈጣሪ አደረገው። ዮሐንስ 1996 .. ተወለደ። እኔ ደግሞ 2001 ላይ ወደ ኢትዮጵያ ሄድኩይላሉ።

የፎቶው ባለመብት, Alemayhu Zenebe

የምስሉ መግለጫ,  ዮሐንስ ክራርን ጨምሮ ሌሎች የዜማ መሳሪያዎችን ይጫወታል

በኢትዮጵያ የአንድ ወር ቆይታቸው በርካታ አካባቢዎችን ረግጠዋል። በርካታ ገዳማትን እና አብያተ ክርስቲያናትን ተሳልመዋል።  ወደ ጣና፣ አክሱም፣ ጎንደር ላሊበላ፣ ደብረዳሞ እና ሌሎች ቦታዎች ተጉዘው በገዳማቱለጸሎታቸው ምላሽ የሰጣቸውንፈጣሪ አመሰግነዋል።  የኦርቶዶክስ ተዋህዶ መነሻቸው ጃማይካውያን የመሠረቱት ቤተ ክርስቲያን መሆኑን አስበው ወደ ሻሽመኔ አቅንተው ጃማይካዎችን ጎብኝተዋል።

ወደ ዮሐንስ እንመለስ።

ቀሲስ ቃላቸውን ጠበቀው ልጃቸው ቤተ ክርስቲያንን እንዲያገለግል ሰጥተውታል።  ልጄ ይህንን ያደርግልኛል ብለው ሳይሆን ቤተ ክርስቲያንን ያገለግላል ብለው ነው የተሳሉት። እግዚያብሔር የለመኑትን ነው ያደረገላቸው. . .የገቡትን ስለት ሰጥተዋል። የሚጠየቁት ነገር የለምይላሉ አቶ ዓለማየሁ።

ልጃቸውበቤተክርስቲያኑ ካሉት ዲያቆናት የሚመረጠው ነውሲሉም ጨምረዋል። ዮሐንስ ቤተ ክርስቲያንን ከልጅነቱ ጀምሮ ያውቃል።   ብሎ ፊደል ቆጥሮ የጀመረው ትምህርት እስከ ዜማ ደርሷል።

ዲያቆን ሆኖ መቀደስ የጀመረው ግን 13 ዓመቱ ነበር። በቤተ ክርስቲያኑ በወር አንድ ጊዜ በሚሰጠው የእንግሊዝኛ ቅዳሴ ላይ መሪ ዲያቆን ሆኖ ማገልገል የጀመረው ያኔ ነው።  ዮሐንስ ትርጉሙን ባይረዳውም በአማርኛ መጻፍ እና ማንበብ ይችላል።  ሆኖም ለድቁና የበቁትን መጽሐፍት ትርጉም በእንግሊዝኛ ይነገረዋል።

ዮሐንስ ዲያቆን ብቻ አይደለም ዘማሪም ነው።  ዘማሪ ብቻ አይደለም፣ ክራር ይገርፋል፣ ማሲንቆም ይጫወታል፣ ከበሮ ይመታል።  ከዚያም አልፎ፣ እንጨት ቆርጦ፣ ክሮችን ወጥሮ ክራር እና ማሲንቆን ይሠራል።  የእሱ ታናናሾችንም ያስተምራል። በዩቲዩብ እና ቲክ ቶክ ላይ የሙዝር እና የዜማ መሳሪያ አጨዋወትን የሚያሳይ ቪዲዮም ይጭናል።

የዮሐንስ ሥራ ብዙ ነው።  ከድምጽ ማጉያው ፊት ቆሞ ምዕመናኑን የሚመስጥ ዜማ ያሰማል። ያ ድምጽ ማጉያ እክል ቢገጥመው ዮሐንስ ይጠግነዋል። በቤተ ክርስቲያን ውስጥየቴክኒክ ችግርካጋጠመ ዮሐንስ አለ። ለዚያ ነው አቶ ዓለማየሁ የዲያቆን የሐንስ ተግባርከሚጠበቀው በላይ ነውየሚሉት።

በጣም ትሁት ነው። ሲታዘዝእሺ፣ ወዴት እንጂ ማን ያዘኛል?’ የሚል ነገር የለውምየሚሉት አቶ ዓለማየሁዮሐንስ [በግዕዝ እና በአማርኛ] ዳዊት፣ ወንጌልና መልዕክቶችን ሲያነብ ብዙ ኢትዮጵያውያን በጣም ይጸጸታሉ።ልጆቻችንን እኛ ሳናስተምር። እሱ ከሌላ ቋንቋ መጥቶ እንዲህ አይነት አገልግሎት ሲሰጥ በራሳችን እናፍራለንይሉናልይላሉ።

በአውሮፕላን ቴክኒሺያንነት የተመረቀ ሲሆን ካልጋሪ በሚገኝ አንድ የአውሮፕላን ኩባንያ እየሠራ ይገኛል። በትምህርቱም የተመሰገነ ነው።  ዮሐንስ ስለ ቤተክርስቲያኑ ሲናገርየኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያንን ካልኖርክበት አትረዳውም. . . እኔ እዚያ ነው ያደግኩት። ሁልጊዜ በየሳምንቱ እሄዳለሁ። የሳምንቱን ጉልበት የማገኘው ከቤተ ክርስቲያን ነውይላል።

“ዮሐንስ  የሶስት ዓመት ልጅ እያለ [አባቱ] ትንሽ ከበሮ ሰርቶለት ሁልጊዜ ከፊት ቆሞ ይዘምር ነበር”

 

 

 

 

 

 

 

የፎቶው ባለመብት, Alemayhu Zenebe

የምስሉ መግለጫ,  ዮሐንስ የሦስት ዓመት ልጅ እያለ [አባቱ] ትንሽ ከበሮ ሰርቶለት ሁልጊዜ ከፊት ቆሞ ይዘምር ነበርአሁን በሥራ ምክንያት ካደገበት ቤተ ክርስቲያን ቢርቅም አገልግሎቱ ግን እንደሚቀጥል ይጠቅሳል።

በምችለው መጠን ቤተ ክርስቲያንን አገለግላለሁ። እርግጠኛ ነኝ ፈጣሪ ለእኔ ያለው ነገር አለ። ማን ያውቃል? ካህን ወይም መነኩሴ እንድሆን ይፈልግ ይሆናል። ዲያቆን የሆንኩት ራሱ በእኔ ዕቅድ አይደለም። በእሱ ዕቅድ እና ባዘጋጀልኝ ነገር እምነት አለኝብሏል።  የንግሥተ ሳባን ታሪክ እጅግ እንደሚወዱት የሚናገሩት ቀሲሱ፣ በንግሥቲቱ ሌላኛው ስም የመጨረሻዋን ልጃቸውንማክዳብለዋታል።  በጥርስ ሕክምና የተመረቀችው ማክዳ በዘማሪነት ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ታገለግላለች።  በግዕዝ እና አማርኛ ቋንቋዎችም ትዘምራለች።

የፎቶው ባለመብት, Alemayhu Zenebe

የምስሉ መግለጫ,  ዲያቆን ዮሐንስ አሎንዞ

ቤተሰቦቼ አእምሮዬ የታመመ መስሏቸው ነበር

ቀሲስ ዳንቴ ወደ ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ሲመጡ ቤተሰቦቻቸውን ለማሳመንእጅግ አስቸጋሪጊዜያትን አሳልፈዋል። እኔ እውነቱ ሲገለጥልኝ እነሱ በተሳሳተ መንገድ ነበር የተረዱኝ። ያበድኩ መስሏቸው ነበር። ጤነኛ እንደሆንኩ ለማረጋገጥ ከመካከላቸው አስቀምጠው ያዋሩኝ ነበር። እንዴት እንደምመልስ፣ እንዴት እንደማወራ ይከታተሉኝ ነበር። በሁለተኛው ጊዜ ደግሞ እኔን ለመርዳት የአእምሮ ጤና ባለሙያ ጋር ደወሉይላሉ።

ቀጥለውቤተሰቦቼ ጃማይካውያኑ ጓደኞቼ የምበላው ምግብ ውስጥ የሆነ ነገር ያደረጉብኝ ነበር የመሰላቸውብለዋል። ነገሩ ካለፈ በኋላ እናታቸው ለቤተሰቦቻቸው የነገሩትን ለዳንቴ ነግረዋቸዋል። እናቴ ለቤተሰቡወንድማችሁ አላበደም። በራሱ ለሕይወቱ እጅግ አስፈላጊ የሆነውና የሚያስደሰተውን ነገር አግኝቷል። ከዚህ ነገር ልታላቅቁት አትቸሉምብላቸዋለችሲሉ ይገልጻሉ።

ቢሆንም እህት እና ወንድሞች አልተስማሙም። በተለይ ከታላቅ ወንድማቸው ከባድ ተቃውሞ ገጥሟቸዋል። ብዙ ውይይት እና ክርክር ማድረጋቸውን ያስታውሳሉ። የተቀየረ ነገር አልነበረም። ሃይማኖት የግል ነውበሚል ቤተሳባዊነቱ ቀጠለ።

እኔ የእነሱን ምርጫ አክበራለሁ፤ እነሱም የእኔን ያከብራሉሲሉ ጠቅሰዋል። የፊሊፒንስ እና የካናዳ ጥምር ዜግነት ያላቸው ቀሲስ ዳንቴ የተከበሩ የእጅ ባለሙያ ናቸው። በኢንዱስትሪ ውስጥ ብረቶችን ቅርጽ እያወጡ ለልዩ ልዩ አገልግሎት ያውላሉ።

አባቴ በቤተ ክርስቲያን ካለው አገልግሎት ባሻገር እጅግ ጎበዝ የእጅ ባለሙያ ነው። ሥራውን ጠንቅቆ ያውቃል። ጥሩ የፈጠራ ችሎታ አለውይላል ዲያቆን ዮሐንስ። በትውልድ አገራቸው ፊሊፒንስ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን የማስገንባት ዕቅድም አላቸው።

ዕቅድ ብቻ ሳይሆን ሥራ ጀምረዋል። 10 ሺህ ካሬ ሜትር መሬት ላይ ቤተክርስቲያን ለማስገንባት የሚሆን መሬት በግላቸው ገዝተዋል።  በአገሬ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶን ማስተዋወቅ እፈልጋለሁ። ሰዎች በዚያ እንዲያመልኩ፣ ወደ እግዚአብሔር መንግሥት እንዲመጡ እፈልጋለሁይላሉ።

ልጃቸው ዮሐንስአባቴ ለሐይማኖታችን እጅግ ታማኝ እና ትጉህ ነውሲል አቶ ዓለማየሁ የዳንቴ ቤተሰብየክርስቶስን መንገድ የተከተሉ ናቸውሲሉ መስክረውላቸዋል። 

ወደ ኢትዮጵያ ዳግም የመመለስ ሀሳብ እንዳላቸው እና አማርኛ መማር እንደሚፈልጉ የሚገልጹት ቀሲስ ዳንቴ ደግሞበኢትዮጵያም ይሁን በቤተ ክርስቲያናችን ብዙ ፈተና እንዳለ አውቃለሁ። ምንም ቢሆን ኢትዮጵያ የእኔ ዕጣ ፈንታ ነች። ለኢትዮጵያ ያለኝ ፍቅር መቼም አይቀየርምብለዋል።