2024 ፌብሩዋሪ 28, ረቡዕ

ስበከት

 

ባለ ዕዳ ልጆቼን ባሪያዎች አድርጎ ሊወስዳቸው መጥቶአልመጽሐፈ ነገሥት ካልዕ 4 1

በዲ/ን ብርሃኑ አድማስ ከዓመታት በፊት በሚሊንየም አዳራሽ ያስተማረው ትምህርት ነው፡፡ ትምህርቱን ስትሰሙት ለዛሬ ጊዜ የቤተክርስቲያን ፈተና ሁሉ ምላሽ የሚሰጥ ፤የሐዲስ ኪዳን ጥላ በሆነው በቡሉይ ኪዳን ዘመን በተፈጸመ ታሪክ ውስጥ፤ የአሁን ዘመን የቤተክርስቲያ ፈተና የሚያሳይ፤  ዲያቢሎስ ልጆቿን ባለዕዳ አድርጎ ሊወስድ ቢሞክርም እንደማይችል፤ ጊዜው ሲያልፍ ፈተናውም እንደሚያልፍ፤ ቤተክርስቲያን የመንፈስ ቅዱስ የጸጋው ግምጃቤት ሆና እንደምትኖር የሚያስረዳ የሚያጽናና ትምህርት ነው፡፡

ከታች ያለውን ማስፈንጠሪያ ተጭነው ይህን ስብከት ያዳምጡ

https://youtu.be/ahg57DS5UP4

3፡28᎓-  መጥታም ለእግዚአብሔር ሰው ነገረችው እርሱም ሄደሽ ዘይትሽን ሽጪ ለባለዕዳውም ክፈይ አንቺና ልጆችሽም ከተረፈው ተገመገቡ አለ

5፡56᎓-  መጽሐፍ ቅዱስ ስናነብ የእሥራኤል መንግስት የሚለው የአሥሩን ነገድ መንግስት ነው፡፡

6፡45᎓- በብሉይ ኪዳን ጊዜ መቅደሱ አንድ ብቻ ነው እርሱም ኢየሩሳሌም ነው በየአውራጃው በየወረዳው የነበረው ሙክራብ ይባላል::

8፡36᎓- አክአብ በጣም ጨካኝ ሚስቱ ኤልዛቤል በትውልዷ ሶርያዊት  ስለነበረች  እግዚአብሔርን ስለማምለክ ከፍተኛ ጥላቻ ነበራት::

10፡02᎓- በዚያን ዘመን ነቢዩ ኤልያስ ነበረ የእግዚአብሔር አምላክነት እንዲታወቅ ሰማይን እና ምድርን ገዘተ::

10፡42᎓- አቡዲዩ የአክአብ ባለሥልጣን ሆኖ በአክአብ ቤተመንግስት እየኖረ መቶ ነቢይነት ትምህርት የሚማሩ ደቀመዛሙርትን ሃምሳውን በአንድ ዋሻ  ሃምሳውን በአንድ ዋሻ  ብቻውን ደብቆ  ማስተማር መመገብ ጀመረ::

17፡36᎓- ባሌ ባርያህ ሞቷል እግዚአብሔርን ይፈራ እንደነበረ አንተ ታውቃለህ::

26፡26᎓- ወደ ኤልሳ የሄደቸው ሴት የቅድስት ቤተ ክርስቲያን ምሳሌ ናት ኤልሳ ደግሞ የጌታችን የአምላካችን የኢየሱስ ክርስቶስ ምሳሌ ነው ልጆቿ ደግሞ የምእመናን ምሳሌዎች ናቸው ባለ ዕዳ የተባለው ደግሞ ዲያብሎስ ነው

28፡23᎓- ቤተክርስቲያን ልጆቿን ለመሥጠት ፈቃደኛ አይደለችም ምንም ያህል ባለእዳዎች ብንሆንም ምንም ያህል ኃጢአተኞች ብንሆን::

ምንም አስተያየቶች የሉም:

አስተያየት ይለጥፉ