-->

ማዕዶት የያዕቆብ ሰንደቁ የጡመራ ገጽ

ማዕዶት የያዕቆብ ሰንደቁ የጡመራ ገጽ

ማዕዶት የያዕቆብ ሰንደቁ የጡመራ ገጽ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት በደብረ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያን እና የአንቀጸ ብፁዓን ሰንበት ትምህርት ቤት ሰባኪ እና መምህር የሆነው የያዕቆብ ሰንደቁ መንፈሳዊ ትምህርቶች እና ወጎች የሚፃፉበት ገጽ ነው፡፡ የዚህ የጡመራ ገጽ ዓላማም በዓለም ዙሪያ ያሉ ሰዎችን ሁሉ ወደ ጽድቅ ወደ መልካም ሥነምግባር እንዲመለሱ ማስተማር ነው፡፡ “ጥበበኞቹም እንደ ሰማይ ፀዳል፥ ብዙ ሰዎችንም ወደ ጽድቅ የሚመልሱ እንደ ከዋክብት ለዘላለም ይደምቃሉ፡፡” ትንቢተ ዳንኤል 12÷3

የኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን ውስጣዊ ክፍል የኢትዮጵያ ከፍተኛ ቦታ የፀሐይ መውጫ የተረጋጋ መንፈሳዊ መንገድ
አዲስ ገጽ

ወግ - መስከረም 1 የዓዲስ ዓመት መባቻ

ገጹን ይመልከቱ

ወግ - የጥር ምሥጢር

 

የጥር  ምሥጢር

ጥር ወር መጨረሻ ነው። የአዲስ አበባ ፀሐይ በኃይል ደምቃ ጭንቅላት ላይ ታቃጥላለች። ሙሽራው ረጅሙን የታክሲ ሰልፍ ተጋፍጦ፣ በላብ ተጠምቆና ራሰ በረሀው አናቱ በፀሐይ ግሏል፤ የባሰ የሚለበልበው ግን በውስጡ የያዘው ምስጢር ነው።  ዛሬ ለባለቤቱ ሳያሳውቅ ወደ አንድ ብድር ተቋም በመሄድ የጋብቻቸውን አምስተኛ ዓመት ለማክበር ብድር ጠይቋል፡፡ ያሰበውን ያህል የብድር መጠን አለማግኘቱ ሳያንስ የሚሠጡት ገንዘብ አነስተኛ መሆኑ አበሳጭቶታል፡፡ ላለፉት ሦስት ወራት አከራዩን አዛውንት ለማምለጥ ሲል፣ እንደ ሌባ በመሽሎክለክ ማታ በጨለማ ነበር ወደ ቤት የሚገባው። ዛሬ ግን አልቀናውም፤ ብረት መዝጊያውን ሲያንኳኳአዛውንቱ ጋር ፊትለፊት ተፋጠጡ።


"አጅሬስትደበቅ ስትደበቅ አገኘሁህ አይደልሦስተኛ ወርህእኮ መጣ!" አሉት አዛውንቱ በደከመ ድምፃቸው። እርሱ ግን "አስተካክላለሁብሎ በድንጋጤ አልፏቸው ወደ ጠባቡ ባለ አንድ መኝታ ክፍል ገባ።

ባለቤቱ የለበሰችው ያረጀ የቤት ልብስና የተዝረከረከው ጸጉሯ የኑሮውን ጫና ይናገራሉ። በእጇ የጨበጠችው ወረቀት ግን መብረቅ ሆነበት። ገና ጋብቻውን ከመመስረቱ አምስት ዓመት በፊት፣ ለሠርጉን ድል አድርጎ ለመደገስ እና ለማድመቂያ ብሎ ደብቆ የተበደረው 300 ሺህ ብር፣ ዛሬ ከነወለዱ 500 ሺህ ብር ሆኖ የክስ መጥሪያ መጣ።

  ሚስት ይህን ዕዳ ፈጽሞ አታውቅም ነበር! ለልጃቸው ወተት የሚገዛበት አጥተው፣ ሚስት ያላትን የወርቅ ሀብልና የጆሮ ጌጥ ሸጣ የዕለት ጉርስ ስትሸፍን፣ እርሱ ግን ከዕዳው ይልቅ ለ"ድንገቴ ፈንጠዝያ" የሚሆን ብድር ፍለጋ ይባክናል። በአምስተኛው ዓመት የጋብቻ በዓላቸው ቀን፣ ለፍቅራቸው መታሰቢያ የሚሆን ስጦታ ሳይሆን፣ ልብሳቸውን የያዙ ሻንጣዎች በሩ ላይ ተደርድረዋል።

አምስተኛው ዓመት በደስታ ሊከበር ሲገባው፣ በአንድ በኩል የአከራዩ ጩኸት፣ በሌላ በኩል የባንክ ክስ፣ መሀል ላይ ደግሞ የወተት ጥያቄ ይዞ የሚያለቅስ ሕፃን። ዛሬ በራቸው የተከፈተው ለመውጫ እንጂ ለደስታ አይመስልም። ገንዘብ እና ጋብቻ ምን እና ምን ናቸው:: ገንዘብን የማስተዳደር ብልሀት ለባለትዳሮች ወሳኝ ይሆን?

 


ምንም አስተያየቶች የሉም:

አስተያየት ይለጥፉ

ማዕዶት አንቀጸ ወራዙት እና የወጣቶች ተግባራዊ ክርስቲያናዊ ሕይወት

ማዕዶት፡- ወደ መንፈሳዊነት አብረን እንሻገር! "ጥበበኞቹም እንደ ሰማይ ፀዳል፥ ብዙ ሰዎችንም ወደ ጽድቅ የሚመልሱ እንደ ከዋክብት  ለዘላለም ይደምቃሉ"  (ትንቢተ ዳንኤል 12÷3) በቤተክርስቲያናችን...

በመምህር ያዕቆብ ሰንደቁ የተዘጋጀ መንፈሳዊ መፃሕፍት

Image 1
Image 2
Image 3
Image 4

የሳምንቱ የመፅሐፍ ቂዱስ ጥቅስ

"በፍጹም ልብህ በእግዚአብሔር ታመን፥ በራስህም ማስተዋል አትደገፍ፤ በመንገድህ ሁሉ እርሱን እወቅ፥ እርሱም መንገድህን ያቀናልሃል።" ምሳሌ 3፡5-6

Video