-->

ማዕዶት የያዕቆብ ሰንደቁ የጡመራ ገጽ

ማዕዶት የያዕቆብ ሰንደቁ የጡመራ ገጽ

ማዕዶት የያዕቆብ ሰንደቁ የጡመራ ገጽ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት በደብረ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያን እና የአንቀጸ ብፁዓን ሰንበት ትምህርት ቤት ሰባኪ እና መምህር የሆነው የያዕቆብ ሰንደቁ መንፈሳዊ ትምህርቶች እና ወጎች የሚፃፉበት ገጽ ነው፡፡ የዚህ የጡመራ ገጽ ዓላማም በዓለም ዙሪያ ያሉ ሰዎችን ሁሉ ወደ ጽድቅ ወደ መልካም ሥነምግባር እንዲመለሱ ማስተማር ነው፡፡ “ጥበበኞቹም እንደ ሰማይ ፀዳል፥ ብዙ ሰዎችንም ወደ ጽድቅ የሚመልሱ እንደ ከዋክብት ለዘላለም ይደምቃሉ፡፡” ትንቢተ ዳንኤል 12÷3

የኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን ውስጣዊ ክፍል የኢትዮጵያ ከፍተኛ ቦታ የፀሐይ መውጫ የተረጋጋ መንፈሳዊ መንገድ
አዲስ ገጽ

አንቀጸ ወራዙት/ወጣቶች/-"የቢራ ጎርፍ"

ገጹን ይመልከቱ

ወግ - የትኛው ይሻልሀል ?

 

የትኛው ይሻልሀል ?

ሰሞኑን ከሜክሲኮ ወደ አራትኪሎ ታክሲ ተሳፍሬ ልክ አራትኪሎ ታክሲ መውረጃው ጋር ስደርስ እንዲህ ሆነ፡፡ ገና ታክሲውን ሲያየው ሰውነቱ በስፖርት የዳበረ ወጠምሻ የታክሲ ተራ አስከባሪ፤ በመስኮት አንገቱን ብቅ ያደረገውን የታክሲ ረዳት “አንተ እንኳንም አገኘሁ” እያለ እሳት ጎርሶ እሳት ለብሶ ወደ ተሳፈርንበት ታክሲ እየሮጠ መጣ፡፡

የታክሲ ረዳቱን ከተራ አስከባሪው የሰውነት ግዝፈት ጋር ሲነፃፀር በዝሆን እግር ስር እንደወደቀች አነስተኛ ነገር ያህል ነበር፡፡ የታክሲው በር ተከፍቶ ተሳፋሪዎች ሲወርዱ ተራ አስከባሪው እጁን ለቡጢ ጨብጦ ፊቱን አኮሳትሮ በፍጥነት ሲመጣ አይ በቃ አይለቀውም አያስተርፈውም ብዬ ሽምቅቅ አልኩኝ፡፡

ረዳቱ የመጣው ይምጣ እንጂ ማን ይፈራል ያለ ይመስላል፡፡ ማስፈራሪያውንም ዛቻውንም ከምንም ሳይቆጥር በእጁ ያያዘውን ገንዘብ ወደ ኪሱ በፍጥነት ከተተው፡፡ ሳይፈራ ኮስተር ብሎ “ና ማን የሚፈራህ መሰለህ” ብሎ የሸሚዙን  እጅ ወደ ላይ ሰቡስቦ በቁመትም በግዝፈት ወደሚበልጠው ተራ አስከባሪ ስር በፍጥነት ሄዶ ተወሽቆ ወደ ላይ ቀና እያለ ያየው ጀመረ፡፡

እኔም በልቤ ሲጣሉ ልገላግል ነው ወይስ ቆሜ ላይ ነው እያልኩኝ ፈዝዤ ቀረሁ፡፡ ተሳፊው እና በአካባቢው ያሉ ሰዎች ሁኔታውን ለማየት አፍጥጠን ቆምን፡፡

ተራ አስከባሪው እስሩ የተወሸቀውን የታክሲ ረዳት አንገቱን እንቅ አድርጎ ወደ ላይ አንጠለጠለው፡፡ እንደገናም መልሶ ወደ መሬት አወረደው እና ደግሞ ደጋግሞ “ተው ብዬህ አልነበረም እንዴ? ዛሬ የመጨረሻ ነው ትመርጣለህ” እያለ ጮኸበት፡፡ ረዳቱም ግራ በመጋባት “ልቀቀኝ እንጂ ምኑን ነው የምመርጠው” እያለ ተወራጨ፡፡

ተራ አስከባሪው በግዙፍ ሰውነቱ ቁልቁል የሚያየውን የታክሲ ረዳት አንገቱን እንዳነቀው “በል ምረጥ እኮ ምረጥ ስድብ ይሻልሀል ወይስ ምክር፤ አሁን እስኪበቃኝ ድረስ ልስደብህ አለበለዛ ደግሞ ልምከርህ ቶሎበል ምረጥ ብሎ ጮሆበት፡፡ ረዳቱ በሁኔታው ተገርሞ “ከሆነማ ብትመክረኝ ይሻለኛል ”ብሎ በረጅሙ ተነፈሰ፡፡

 ለአጭር ደቂቃ የሆነ ክስተት አስገራሚ ነበር፡፡ ይሄ የታክሲ ረዳት “ደግ ጉልበተኛ ላይ ይጣልህ” የሚል ምርቃት ደርሶለታል መሰለኝ ያሁሉ ድንፋታ በምክር ተቀየረለት፡፡ እኛም እንገላግላለን ብለን ቡጡ ሳንቀምስ ስድቡንም ሳንሰማ ወደ ጉዳያችን ሄድን፡፡

ወዳጄ ከጉልበተኛ መካከል ለካ የሚራራ አስተዋይም ይገኛል፡፡ በዓለም ስንት ጉልበተኛ አለ መሳለህ እንደፈለገ የሚያንጠለጥልህ ወደ ግራ ወደ ቀኝ የሚወዘውዝህ፡፡ እናም እንደዚህ የታክሲ ረዳት ደገኛውን ይስጥህ እንጂ አስመርጦ የሚቀጣህ፡፡ ለአንተ ግን የትኛው ይሻልሀል ? ከቁጣ፣ ከስድብ፣ ከዱላ ምክር አይሻልም !

  “በመልካም ሥርዓት ሰልፍ ታደርጋለህ፤ድልም ብዙ ምክር ባለበት ዘንድ ነው፡፡” መጽሐፈ ምሳሌ 24÷6

ያዕቆብ ሰንደቁ

መጋቢት 1 ቀን 2015

ምንም አስተያየቶች የሉም:

አስተያየት ይለጥፉ

ማዕዶት አንቀጸ ወራዙት እና የወጣቶች ተግባራዊ ክርስቲያናዊ ሕይወት

ማዕዶት፡- ወደ መንፈሳዊነት አብረን እንሻገር! "ጥበበኞቹም እንደ ሰማይ ፀዳል፥ ብዙ ሰዎችንም ወደ ጽድቅ የሚመልሱ እንደ ከዋክብት  ለዘላለም ይደምቃሉ"  (ትንቢተ ዳንኤል 12÷3) በቤተክርስቲያናችን...

በመምህር ያዕቆብ ሰንደቁ የተዘጋጀ መንፈሳዊ መፃሕፍት

Image 1
Image 2
Image 3
Image 4

የሳምንቱ የመፅሐፍ ቂዱስ ጥቅስ

"በፍጹም ልብህ በእግዚአብሔር ታመን፥ በራስህም ማስተዋል አትደገፍ፤ በመንገድህ ሁሉ እርሱን እወቅ፥ እርሱም መንገድህን ያቀናልሃል።" ምሳሌ 3፡5-6

Video